क़ुरआन के अर्थों का अनुवाद - अम्हारी अनुवाद * - अनुवादों की सूची

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

अर्थों का अनुवाद सूरा: सूरा अश्-शु-अ़-रा   आयत:

ሱረቱ አሽ ሹዐራእ

طسٓمٓ
ጧ ሲን ሚም
अरबी तफ़सीरें:
تِلۡكَ ءَايَٰتُ ٱلۡكِتَٰبِ ٱلۡمُبِينِ
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
لَعَلَّكَ بَٰخِعٞ نَّفۡسَكَ أَلَّا يَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِن نَّشَأۡ نُنَزِّلۡ عَلَيۡهِم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ ءَايَةٗ فَظَلَّتۡ أَعۡنَٰقُهُمۡ لَهَا خَٰضِعِينَ
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ።
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا يَأۡتِيهِم مِّن ذِكۡرٖ مِّنَ ٱلرَّحۡمَٰنِ مُحۡدَثٍ إِلَّا كَانُواْ عَنۡهُ مُعۡرِضِينَ
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَقَدۡ كَذَّبُواْ فَسَيَأۡتِيهِمۡ أَنۢبَٰٓؤُاْ مَا كَانُواْ بِهِۦ يَسۡتَهۡزِءُونَ
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَوَلَمۡ يَرَوۡاْ إِلَى ٱلۡأَرۡضِ كَمۡ أَنۢبَتۡنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوۡجٖ كَرِيمٍ
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን?፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِذۡ نَادَىٰ رَبُّكَ مُوسَىٰٓ أَنِ ٱئۡتِ ٱلۡقَوۡمَ ٱلظَّٰلِمِينَ
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡
अरबी तफ़सीरें:
قَوۡمَ فِرۡعَوۡنَۚ أَلَا يَتَّقُونَ
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبِّ إِنِّيٓ أَخَافُ أَن يُكَذِّبُونِ
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَيَضِيقُ صَدۡرِي وَلَا يَنطَلِقُ لِسَانِي فَأَرۡسِلۡ إِلَىٰ هَٰرُونَ
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَهُمۡ عَلَيَّ ذَنۢبٞ فَأَخَافُ أَن يَقۡتُلُونِ
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ كَلَّاۖ فَٱذۡهَبَا بِـَٔايَٰتِنَآۖ إِنَّا مَعَكُم مُّسۡتَمِعُونَ
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأۡتِيَا فِرۡعَوۡنَ فَقُولَآ إِنَّا رَسُولُ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَنۡ أَرۡسِلۡ مَعَنَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ أَلَمۡ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدٗا وَلَبِثۡتَ فِينَا مِنۡ عُمُرِكَ سِنِينَ
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን? በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን?
अरबी तफ़सीरें:
وَفَعَلۡتَ فَعۡلَتَكَ ٱلَّتِي فَعَلۡتَ وَأَنتَ مِنَ ٱلۡكَٰفِرِينَ
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን? አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ فَعَلۡتُهَآ إِذٗا وَأَنَا۠ مِنَ ٱلضَّآلِّينَ
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَفَرَرۡتُ مِنكُمۡ لَمَّا خِفۡتُكُمۡ فَوَهَبَ لِي رَبِّي حُكۡمٗا وَجَعَلَنِي مِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَتِلۡكَ نِعۡمَةٞ تَمُنُّهَا عَلَيَّ أَنۡ عَبَّدتَّ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ فِرۡعَوۡنُ وَمَا رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው?»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَآۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ لِمَنۡ حَوۡلَهُۥٓ أَلَا تَسۡتَمِعُونَ
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን?» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبُّكُمۡ وَرَبُّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ إِنَّ رَسُولَكُمُ ٱلَّذِيٓ أُرۡسِلَ إِلَيۡكُمۡ لَمَجۡنُونٞ
(ፈርዖን) "ያ ወደናንተ የተላከው መልእክተኛችሁ በእርግጥ እብድ ነው" አለ።
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقِ وَٱلۡمَغۡرِبِ وَمَا بَيۡنَهُمَآۖ إِن كُنتُمۡ تَعۡقِلُونَ
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ لَئِنِ ٱتَّخَذۡتَ إِلَٰهًا غَيۡرِي لَأَجۡعَلَنَّكَ مِنَ ٱلۡمَسۡجُونِينَ
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ أَوَلَوۡ جِئۡتُكَ بِشَيۡءٖ مُّبِينٖ
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ?» አለው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ فَأۡتِ بِهِۦٓ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَلۡقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعۡبَانٞ مُّبِينٞ
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَنَزَعَ يَدَهُۥ فَإِذَا هِيَ بَيۡضَآءُ لِلنَّٰظِرِينَ
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ لِلۡمَلَإِ حَوۡلَهُۥٓ إِنَّ هَٰذَا لَسَٰحِرٌ عَلِيمٞ
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
يُرِيدُ أَن يُخۡرِجَكُم مِّنۡ أَرۡضِكُم بِسِحۡرِهِۦ فَمَاذَا تَأۡمُرُونَ
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ?» (አላቸው)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالُوٓاْ أَرۡجِهۡ وَأَخَاهُ وَٱبۡعَثۡ فِي ٱلۡمَدَآئِنِ حَٰشِرِينَ
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
يَأۡتُوكَ بِكُلِّ سَحَّارٍ عَلِيمٖ
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
فَجُمِعَ ٱلسَّحَرَةُ لِمِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَقِيلَ لِلنَّاسِ هَلۡ أَنتُم مُّجۡتَمِعُونَ
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን?» ተባለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
لَعَلَّنَا نَتَّبِعُ ٱلسَّحَرَةَ إِن كَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَلَمَّا جَآءَ ٱلسَّحَرَةُ قَالُواْ لِفِرۡعَوۡنَ أَئِنَّ لَنَا لَأَجۡرًا إِن كُنَّا نَحۡنُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን?» አሉት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ نَعَمۡ وَإِنَّكُمۡ إِذٗا لَّمِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ لَهُم مُّوسَىٰٓ أَلۡقُواْ مَآ أَنتُم مُّلۡقُونَ
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَلۡقَوۡاْ حِبَالَهُمۡ وَعِصِيَّهُمۡ وَقَالُواْ بِعِزَّةِ فِرۡعَوۡنَ إِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَلۡقَىٰ مُوسَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ تَلۡقَفُ مَا يَأۡفِكُونَ
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأُلۡقِيَ ٱلسَّحَرَةُ سَٰجِدِينَ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالُوٓاْ ءَامَنَّا بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ ءَامَنتُمۡ لَهُۥ قَبۡلَ أَنۡ ءَاذَنَ لَكُمۡۖ إِنَّهُۥ لَكَبِيرُكُمُ ٱلَّذِي عَلَّمَكُمُ ٱلسِّحۡرَ فَلَسَوۡفَ تَعۡلَمُونَۚ لَأُقَطِّعَنَّ أَيۡدِيَكُمۡ وَأَرۡجُلَكُم مِّنۡ خِلَٰفٖ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمۡ أَجۡمَعِينَ
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን? እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ لَا ضَيۡرَۖ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا مُنقَلِبُونَ
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّا نَطۡمَعُ أَن يَغۡفِرَ لَنَا رَبُّنَا خَطَٰيَٰنَآ أَن كُنَّآ أَوَّلَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
۞ وَأَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنۡ أَسۡرِ بِعِبَادِيٓ إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَرۡسَلَ فِرۡعَوۡنُ فِي ٱلۡمَدَآئِنِ حَٰشِرِينَ
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ هَٰٓؤُلَآءِ لَشِرۡذِمَةٞ قَلِيلُونَ
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّهُمۡ لَنَا لَغَآئِظُونَ
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَٰذِرُونَ
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَخۡرَجۡنَٰهُم مِّن جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَكُنُوزٖ وَمَقَامٖ كَرِيمٖ
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَٰلِكَۖ وَأَوۡرَثۡنَٰهَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَتۡبَعُوهُم مُّشۡرِقِينَ
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَلَمَّا تَرَٰٓءَا ٱلۡجَمۡعَانِ قَالَ أَصۡحَٰبُ مُوسَىٰٓ إِنَّا لَمُدۡرَكُونَ
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ (የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ كَلَّآۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنِ ٱضۡرِب بِّعَصَاكَ ٱلۡبَحۡرَۖ فَٱنفَلَقَ فَكَانَ كُلُّ فِرۡقٖ كَٱلطَّوۡدِ ٱلۡعَظِيمِ
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَأَزۡلَفۡنَا ثَمَّ ٱلۡأٓخَرِينَ
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَأَنجَيۡنَا مُوسَىٰ وَمَن مَّعَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱتۡلُ عَلَيۡهِمۡ نَبَأَ إِبۡرَٰهِيمَ
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَا تَعۡبُدُونَ
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ نَعۡبُدُ أَصۡنَامٗا فَنَظَلُّ لَهَا عَٰكِفِينَ
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ هَلۡ يَسۡمَعُونَكُمۡ إِذۡ تَدۡعُونَ
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን?
अरबी तफ़सीरें:
أَوۡ يَنفَعُونَكُمۡ أَوۡ يَضُرُّونَ
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን?»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ بَلۡ وَجَدۡنَآ ءَابَآءَنَا كَذَٰلِكَ يَفۡعَلُونَ
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ أَفَرَءَيۡتُم مَّا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُمُ ٱلۡأَقۡدَمُونَ
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
فَإِنَّهُمۡ عَدُوّٞ لِّيٓ إِلَّا رَبَّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ٱلَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهۡدِينِ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلَّذِي هُوَ يُطۡعِمُنِي وَيَسۡقِينِ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِذَا مَرِضۡتُ فَهُوَ يَشۡفِينِ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحۡيِينِ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلَّذِيٓ أَطۡمَعُ أَن يَغۡفِرَ لِي خَطِيٓـَٔتِي يَوۡمَ ٱلدِّينِ
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
رَبِّ هَبۡ لِي حُكۡمٗا وَأَلۡحِقۡنِي بِٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱجۡعَل لِّي لِسَانَ صِدۡقٖ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱجۡعَلۡنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ ٱلنَّعِيمِ
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱغۡفِرۡ لِأَبِيٓ إِنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلضَّآلِّينَ
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا تُخۡزِنِي يَوۡمَ يُبۡعَثُونَ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
يَوۡمَ لَا يَنفَعُ مَالٞ وَلَا بَنُونَ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِلَّا مَنۡ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلۡبٖ سَلِيمٖ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
وَأُزۡلِفَتِ ٱلۡجَنَّةُ لِلۡمُتَّقِينَ
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِلۡغَاوِينَ
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَقِيلَ لَهُمۡ أَيۡنَ مَا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
अरबी तफ़सीरें:
مِن دُونِ ٱللَّهِ هَلۡ يَنصُرُونَكُمۡ أَوۡ يَنتَصِرُونَ
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን?»
अरबी तफ़सीरें:
فَكُبۡكِبُواْ فِيهَا هُمۡ وَٱلۡغَاوُۥنَ
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَجُنُودُ إِبۡلِيسَ أَجۡمَعُونَ
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ وَهُمۡ فِيهَا يَخۡتَصِمُونَ
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
अरबी तफ़सीरें:
تَٱللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَٰلٖ مُّبِينٍ
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَضَلَّنَآ إِلَّا ٱلۡمُجۡرِمُونَ
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَمَا لَنَا مِن شَٰفِعِينَ
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٖ
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَلَوۡ أَنَّ لَنَا كَرَّةٗ فَنَكُونَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህ እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَّبَتۡ قَوۡمُ نُوحٍ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
۞ قَالُوٓاْ أَنُؤۡمِنُ لَكَ وَٱتَّبَعَكَ ٱلۡأَرۡذَلُونَ
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን?» አሉት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ وَمَا عِلۡمِي بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنۡ حِسَابُهُمۡ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّيۖ لَوۡ تَشۡعُرُونَ
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَنَا۠ بِطَارِدِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنۡ أَنَا۠ إِلَّا نَذِيرٞ مُّبِينٞ
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ لَئِن لَّمۡ تَنتَهِ يَٰنُوحُ لَتَكُونَنَّ مِنَ ٱلۡمَرۡجُومِينَ
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبِّ إِنَّ قَوۡمِي كَذَّبُونِ
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱفۡتَحۡ بَيۡنِي وَبَيۡنَهُمۡ فَتۡحٗا وَنَجِّنِي وَمَن مَّعِيَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
فَأَنجَيۡنَٰهُ وَمَن مَّعَهُۥ فِي ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا بَعۡدُ ٱلۡبَاقِينَ
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸው አማኞች አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَّبَتۡ عَادٌ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ هُودٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَتَبۡنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ ءَايَةٗ تَعۡبَثُونَ
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمۡ تَخۡلُدُونَ
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
وَإِذَا بَطَشۡتُم بَطَشۡتُمۡ جَبَّارِينَ
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱتَّقُواْ ٱلَّذِيٓ أَمَدَّكُم بِمَا تَعۡلَمُونَ
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَمَدَّكُم بِأَنۡعَٰمٖ وَبَنِينَ
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَجَنَّٰتٖ وَعُيُونٍ
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّيٓ أَخَافُ عَلَيۡكُمۡ عَذَابَ يَوۡمٍ عَظِيمٖ
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ سَوَآءٌ عَلَيۡنَآ أَوَعَظۡتَ أَمۡ لَمۡ تَكُن مِّنَ ٱلۡوَٰعِظِينَ
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا خُلُقُ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَكَذَّبُوهُ فَأَهۡلَكۡنَٰهُمۡۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ صَٰلِحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን ?
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَتُتۡرَكُونَ فِي مَا هَٰهُنَآ ءَامِنِينَ
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
فِي جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَزُرُوعٖ وَنَخۡلٖ طَلۡعُهَا هَضِيمٞ
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
अरबी तफ़सीरें:
وَتَنۡحِتُونَ مِنَ ٱلۡجِبَالِ بُيُوتٗا فَٰرِهِينَ
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا تُطِيعُوٓاْ أَمۡرَ ٱلۡمُسۡرِفِينَ
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ٱلَّذِينَ يُفۡسِدُونَ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَلَا يُصۡلِحُونَ
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُوٓاْ إِنَّمَآ أَنتَ مِنَ ٱلۡمُسَحَّرِينَ
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
مَآ أَنتَ إِلَّا بَشَرٞ مِّثۡلُنَا فَأۡتِ بِـَٔايَةٍ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ هَٰذِهِۦ نَاقَةٞ لَّهَا شِرۡبٞ وَلَكُمۡ شِرۡبُ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوٓءٖ فَيَأۡخُذَكُمۡ عَذَابُ يَوۡمٍ عَظِيمٖ
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
فَعَقَرُوهَا فَأَصۡبَحُواْ نَٰدِمِينَ
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَخَذَهُمُ ٱلۡعَذَابُۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَّبَتۡ قَوۡمُ لُوطٍ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَتَأۡتُونَ ٱلذُّكۡرَانَ مِنَ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمۡ رَبُّكُم مِّنۡ أَزۡوَٰجِكُمۚ بَلۡ أَنتُمۡ قَوۡمٌ عَادُونَ
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን? በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ لَئِن لَّمۡ تَنتَهِ يَٰلُوطُ لَتَكُونَنَّ مِنَ ٱلۡمُخۡرَجِينَ
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ إِنِّي لِعَمَلِكُم مِّنَ ٱلۡقَالِينَ
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
رَبِّ نَجِّنِي وَأَهۡلِي مِمَّا يَعۡمَلُونَ
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
فَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَأَمۡطَرۡنَا عَلَيۡهِم مَّطَرٗاۖ فَسَآءَ مَطَرُ ٱلۡمُنذَرِينَ
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህ እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَّبَ أَصۡحَٰبُ لۡـَٔيۡكَةِ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
अरबी तफ़सीरें:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ شُعَيۡبٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
अरबी तफ़सीरें:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
۞ أَوۡفُواْ ٱلۡكَيۡلَ وَلَا تَكُونُواْ مِنَ ٱلۡمُخۡسِرِينَ
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَزِنُواْ بِٱلۡقِسۡطَاسِ ٱلۡمُسۡتَقِيمِ
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا تَبۡخَسُواْ ٱلنَّاسَ أَشۡيَآءَهُمۡ وَلَا تَعۡثَوۡاْ فِي ٱلۡأَرۡضِ مُفۡسِدِينَ
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱتَّقُواْ ٱلَّذِي خَلَقَكُمۡ وَٱلۡجِبِلَّةَ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُوٓاْ إِنَّمَآ أَنتَ مِنَ ٱلۡمُسَحَّرِينَ
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَنتَ إِلَّا بَشَرٞ مِّثۡلُنَا وَإِن نَّظُنُّكَ لَمِنَ ٱلۡكَٰذِبِينَ
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَأَسۡقِطۡ عَلَيۡنَا كِسَفٗا مِّنَ ٱلسَّمَآءِ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
अरबी तफ़सीरें:
قَالَ رَبِّيٓ أَعۡلَمُ بِمَا تَعۡمَلُونَ
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَهُمۡ عَذَابُ يَوۡمِ ٱلظُّلَّةِۚ إِنَّهُۥ كَانَ عَذَابَ يَوۡمٍ عَظِيمٍ
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّهُۥ لَتَنزِيلُ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
نَزَلَ بِهِ ٱلرُّوحُ ٱلۡأَمِينُ
እርሱን ታማኙ ጂብሪል አወረደው፤
अरबी तफ़सीरें:
عَلَىٰ قَلۡبِكَ لِتَكُونَ مِنَ ٱلۡمُنذِرِينَ
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
بِلِسَانٍ عَرَبِيّٖ مُّبِينٖ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَإِنَّهُۥ لَفِي زُبُرِ ٱلۡأَوَّلِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَوَلَمۡ يَكُن لَّهُمۡ ءَايَةً أَن يَعۡلَمَهُۥ عُلَمَٰٓؤُاْ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን?
अरबी तफ़सीरें:
وَلَوۡ نَزَّلۡنَٰهُ عَلَىٰ بَعۡضِ ٱلۡأَعۡجَمِينَ
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
अरबी तफ़सीरें:
فَقَرَأَهُۥ عَلَيۡهِم مَّا كَانُواْ بِهِۦ مُؤۡمِنِينَ
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
अरबी तफ़सीरें:
كَذَٰلِكَ سَلَكۡنَٰهُ فِي قُلُوبِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
لَا يُؤۡمِنُونَ بِهِۦ حَتَّىٰ يَرَوُاْ ٱلۡعَذَابَ ٱلۡأَلِيمَ
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَيَأۡتِيَهُم بَغۡتَةٗ وَهُمۡ لَا يَشۡعُرُونَ
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَيَقُولُواْ هَلۡ نَحۡنُ مُنظَرُونَ
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን?» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
በቅጣታችን ያቻኩላሉን?
अरबी तफ़सीरें:
أَفَرَءَيۡتَ إِن مَّتَّعۡنَٰهُمۡ سِنِينَ
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ جَآءَهُم مَّا كَانُواْ يُوعَدُونَ
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
अरबी तफ़सीरें:
مَآ أَغۡنَىٰ عَنۡهُم مَّا كَانُواْ يُمَتَّعُونَ
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَهۡلَكۡنَا مِن قَرۡيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ذِكۡرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا تَنَزَّلَتۡ بِهِ ٱلشَّيَٰطِينُ
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا يَنۢبَغِي لَهُمۡ وَمَا يَسۡتَطِيعُونَ
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّهُمۡ عَنِ ٱلسَّمۡعِ لَمَعۡزُولُونَ
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَلَا تَدۡعُ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ فَتَكُونَ مِنَ ٱلۡمُعَذَّبِينَ
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَأَنذِرۡ عَشِيرَتَكَ ٱلۡأَقۡرَبِينَ
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱخۡفِضۡ جَنَاحَكَ لِمَنِ ٱتَّبَعَكَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
فَإِنۡ عَصَوۡكَ فَقُلۡ إِنِّي بَرِيٓءٞ مِّمَّا تَعۡمَلُونَ
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡعَزِيزِ ٱلرَّحِيمِ
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
ٱلَّذِي يَرَىٰكَ حِينَ تَقُومُ
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَتَقَلُّبَكَ فِي ٱلسَّٰجِدِينَ
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
अरबी तफ़सीरें:
هَلۡ أُنَبِّئُكُمۡ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ ٱلشَّيَٰطِينُ
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን?
अरबी तफ़सीरें:
تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٖ
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
يُلۡقُونَ ٱلسَّمۡعَ وَأَكۡثَرُهُمۡ كَٰذِبُونَ
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلشُّعَرَآءُ يَتَّبِعُهُمُ ٱلۡغَاوُۥنَ
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
अरबी तफ़सीरें:
أَلَمۡ تَرَ أَنَّهُمۡ فِي كُلِّ وَادٖ يَهِيمُونَ
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን?
अरबी तफ़सीरें:
وَأَنَّهُمۡ يَقُولُونَ مَا لَا يَفۡعَلُونَ
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
अरबी तफ़सीरें:
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ وَذَكَرُواْ ٱللَّهَ كَثِيرٗا وَٱنتَصَرُواْ مِنۢ بَعۡدِ مَا ظُلِمُواْۗ وَسَيَعۡلَمُ ٱلَّذِينَ ظَلَمُوٓاْ أَيَّ مُنقَلَبٖ يَنقَلِبُونَ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
अरबी तफ़सीरें:
 
अर्थों का अनुवाद सूरा: सूरा अश्-शु-अ़-रा
सूरों की सूची पृष्ठ संख्या
 
क़ुरआन के अर्थों का अनुवाद - अम्हारी अनुवाद - अनुवादों की सूची

पवित्र क़ुरआन के अर्थों का अमहरी अनुवाद, अनुवादक : शैख़ मुहम्मद सादिक़ तथा मुहम्मद सानी हबीब। संशोधन का काम रुव्वाद अनुवाद केंद्र की निगरानी में संपन्न हुआ। मूल अनुवाद सुझाव प्राप्त करने तथा मूल्यांकन एवं निरंतर उन्नयन हेतु उपलब्ध है।

बंद करें