Check out the new design

పవిత్ర ఖురాన్ యొక్క భావార్థాల అనువాదం - అమ్హారిక్ అనువాదం - ఆఫ్రికా అకాడమీ * - అనువాదాల విషయసూచిక


భావార్ధాల అనువాదం సూరహ్: అల్-ఫుర్ఖాన్   వచనం:
وَٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ ءَالِهَةٗ لَّا يَخۡلُقُونَ شَيۡـٔٗا وَهُمۡ يُخۡلَقُونَ وَلَا يَمۡلِكُونَ لِأَنفُسِهِمۡ ضَرّٗا وَلَا نَفۡعٗا وَلَا يَمۡلِكُونَ مَوۡتٗا وَلَا حَيَوٰةٗ وَلَا نُشُورٗا
3. ከሓዲያን ከእርሱ ከአላህ ሌላ ምንንም የማይፈጥሩንና እነርሱ ራሳቸው የሚፈጠሩ፤ ለነፍሶቻቸዉም (ከራሳቸው ላይ) ጉዳትን መከላከልም ሆነ ለራሳቸው ጥቅምን ማምጣት (ማስከበር) የማይችሉ፤ ለሞት ማብቃትም ሆነ ህይወትን መለገስና ከሞት መቀስቀስንም የማይችሉን አማልክትን አምላክ አድርገው ያዙ።
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّآ إِفۡكٌ ٱفۡتَرَىٰهُ وَأَعَانَهُۥ عَلَيۡهِ قَوۡمٌ ءَاخَرُونَۖ فَقَدۡ جَآءُو ظُلۡمٗا وَزُورٗا
4. እነዚያ በአላህ የካዱ ሰዎች «ይህ ቁርኣን እርሱ (ሙሐመድ) በራሱ የቀጠፈውና በእርሱም ላይ ሌሎች ህዝቦች ያገዙት ውሸት እንጂ ሌላ አይደለም።» አሉ። በእርግጥም በደልንና እብለትን ፈጸሙ።
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
وَقَالُوٓاْ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ ٱكۡتَتَبَهَا فَهِيَ تُمۡلَىٰ عَلَيۡهِ بُكۡرَةٗ وَأَصِيلٗا
5. «እነዚህ የመጀመሪያ ሰዎች ተረቶች (አፈታሪክ) ናቸው። አስጽፎታል፤ እናም በእርሱ ላይ ጧትና ማታ ትነበብለታለች።» አሉ።
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
قُلۡ أَنزَلَهُ ٱلَّذِي يَعۡلَمُ ٱلسِّرَّ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ إِنَّهُۥ كَانَ غَفُورٗا رَّحِيمٗا
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው:: እርሱ መሓሪና አዛኝ ነውና።» በላቸው።
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
وَقَالُواْ مَالِ هَٰذَا ٱلرَّسُولِ يَأۡكُلُ ٱلطَّعَامَ وَيَمۡشِي فِي ٱلۡأَسۡوَاقِ لَوۡلَآ أُنزِلَ إِلَيۡهِ مَلَكٞ فَيَكُونَ مَعَهُۥ نَذِيرًا
7. አሉም: «ይህ መልዕክተኛ ምን አይነት መልዕክተኛ ነው? ምግብ የሚመገብ ወደ ገበያ የሚመላለስ፤ ከእርሱ ጋር አስፈራሪ ይሆን ዘንድ ወደ እርሱ መልአክ (በገሃድ) አይወረድም ኖሯልን?
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
أَوۡ يُلۡقَىٰٓ إِلَيۡهِ كَنزٌ أَوۡ تَكُونُ لَهُۥ جَنَّةٞ يَأۡكُلُ مِنۡهَاۚ وَقَالَ ٱلظَّٰلِمُونَ إِن تَتَّبِعُونَ إِلَّا رَجُلٗا مَّسۡحُورًا
8. «ወይም ወደ እርሱ ድልብ አይሰጠዉምን? ወይም ከእርሷ የሚበላባት አትክልት ለእርሱ አትኖረዉምን?» አሉ። «በዳዮችም ላመኑት የተደገመበትን ሰው እንጂ ሌላን አትከተሉም።» አሉ።
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
ٱنظُرۡ كَيۡفَ ضَرَبُواْ لَكَ ٱلۡأَمۡثَٰلَ فَضَلُّواْ فَلَا يَسۡتَطِيعُونَ سَبِيلٗا
9.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ላንተ ምሳሌዎችን እንዴት እንዳደረጉልህና ከዚያም እንዴት እንደ ተሳሳቱ ተመልከት:: ወደ እውነት ለመድረስ መንገድንም አይችሉም::
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
تَبَارَكَ ٱلَّذِيٓ إِن شَآءَ جَعَلَ لَكَ خَيۡرٗا مِّن ذَٰلِكَ جَنَّٰتٖ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ وَيَجۡعَل لَّكَ قُصُورَۢا
10. ያ ቢሻ ከዚህ ካሉት የተሻለን ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው አትክልት ስፍራዎችን ላንተ የሚያደርግልህ ህንጻ ቤቶችንም የሚያደርግልህ የሆነው ጌታ ችሮታው በዛ:: (ክብሩ ላቀ)
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
بَلۡ كَذَّبُواْ بِٱلسَّاعَةِۖ وَأَعۡتَدۡنَا لِمَن كَذَّبَ بِٱلسَّاعَةِ سَعِيرًا
11. ይልቁንም እነርሱ በትንሳኤ አስተባበሉ:: በትንሳኤ ላስተባበለም ሁሉ አቃጣይ እሳት አዘጋጅተናል::
అరబీ భాషలోని ఖుర్ఆన్ వ్యాఖ్యానాలు:
 
భావార్ధాల అనువాదం సూరహ్: అల్-ఫుర్ఖాన్
సూరాల విషయసూచిక పేజీ నెంబరు
 
పవిత్ర ఖురాన్ యొక్క భావార్థాల అనువాదం - అమ్హారిక్ అనువాదం - ఆఫ్రికా అకాడమీ - అనువాదాల విషయసూచిక

దాని అనువాదము మహ్మద్ జీన్ జహ్రుద్దీన్. ఆఫ్రికా అకాడమీ నుండి విడుదల.

మూసివేయటం