قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ * - ترجمے کی لسٹ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ عبَسْ   آیت:

ሱረቱ ዐበሰ

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
عربی تفاسیر:
أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
عربی تفاسیر:
وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
عربی تفاسیر:
أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
عربی تفاسیر:
أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤
عربی تفاسیر:
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
عربی تفاسیر:
وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
عربی تفاسیر:
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
عربی تفاسیر:
وَهُوَ يَخۡشَىٰ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
عربی تفاسیر:
فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
عربی تفاسیر:
كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
عربی تفاسیر:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
عربی تفاسیر:
فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
عربی تفاسیر:
مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
عربی تفاسیر:
بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
عربی تفاسیر:
كِرَامِۭ بَرَرَةٖ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
عربی تفاسیر:
قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
عربی تفاسیر:
مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
عربی تفاسیر:
مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
عربی تفاسیر:
كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
عربی تفاسیر:
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
عربی تفاسیر:
أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
عربی تفاسیر:
فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
عربی تفاسیر:
وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا
ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤
عربی تفاسیر:
وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
عربی تفاسیر:
وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
عربی تفاسیر:
وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
عربی تفاسیر:
مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
عربی تفاسیر:
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
عربی تفاسیر:
يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
عربی تفاسیر:
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
ከናቱም ካባቱም፤
عربی تفاسیر:
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
ከሚስቱም ከልጁም፤
عربی تفاسیر:
لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
عربی تفاسیر:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
عربی تفاسیر:
ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
عربی تفاسیر:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
عربی تفاسیر:
تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
عربی تفاسیر:
أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
عربی تفاسیر:
 
معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ عبَسْ
سورتوں کی لسٹ صفحہ نمبر
 
قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ - ترجمے کی لسٹ

قرآن کریم کے معانی کا امہری زبان میں ترجمہ: شیخ محمد صادق اور محمد الثانی حبیب نے کیا ہے۔ ترجمہ کی تصحیح مرکز رُواد الترجمہ کی جانب سے کی گئی ہے، ساتھ ہی اظہارِ رائے، تقییم اور مسلسل بہتری کے لیے اصل ترجمہ بھی باقی رکھا گیا ہے ۔

بند کریں