Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Dịch thuật tiếng Amharic * - Mục lục các bản dịch

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Al-Qalam   Câu:

ሱረቱ አል ቀለም

نٓۚ وَٱلۡقَلَمِ وَمَا يَسۡطُرُونَ
ኑን፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَآ أَنتَ بِنِعۡمَةِ رَبِّكَ بِمَجۡنُونٖ
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّ لَكَ لَأَجۡرًا غَيۡرَ مَمۡنُونٖ
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٖ
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَسَتُبۡصِرُ وَيُبۡصِرُونَ
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بِأَييِّكُمُ ٱلۡمَفۡتُونُ
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِٱلۡمُهۡتَدِينَ
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَدُّواْ لَوۡ تُدۡهِنُ فَيُدۡهِنُونَ
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافٖ مَّهِينٍ
መሃለኛን ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
هَمَّازٖ مَّشَّآءِۭ بِنَمِيمٖ
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَّنَّاعٖ لِّلۡخَيۡرِ مُعۡتَدٍ أَثِيمٍ
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عُتُلِّۭ بَعۡدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَن كَانَ ذَا مَالٖ وَبَنِينَ
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلۡخُرۡطُومِ
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا بَلَوۡنَٰهُمۡ كَمَا بَلَوۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ إِذۡ أَقۡسَمُواْ لَيَصۡرِمُنَّهَا مُصۡبِحِينَ
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَا يَسۡتَثۡنُونَ
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَطَافَ عَلَيۡهَا طَآئِفٞ مِّن رَّبِّكَ وَهُمۡ نَآئِمُونَ
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَصۡبَحَتۡ كَٱلصَّرِيمِ
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَتَنَادَوۡاْ مُصۡبِحِينَ
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَنِ ٱغۡدُواْ عَلَىٰ حَرۡثِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰرِمِينَ
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱنطَلَقُواْ وَهُمۡ يَتَخَٰفَتُونَ
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَن لَّا يَدۡخُلَنَّهَا ٱلۡيَوۡمَ عَلَيۡكُم مِّسۡكِينٞ
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَغَدَوۡاْ عَلَىٰ حَرۡدٖ قَٰدِرِينَ
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلَمَّا رَأَوۡهَا قَالُوٓاْ إِنَّا لَضَآلُّونَ
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالَ أَوۡسَطُهُمۡ أَلَمۡ أَقُل لَّكُمۡ لَوۡلَا تُسَبِّحُونَ
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالُواْ سُبۡحَٰنَ رَبِّنَآ إِنَّا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَلَٰوَمُونَ
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالُواْ يَٰوَيۡلَنَآ إِنَّا كُنَّا طَٰغِينَ
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عَسَىٰ رَبُّنَآ أَن يُبۡدِلَنَا خَيۡرٗا مِّنۡهَآ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا رَٰغِبُونَ
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
كَذَٰلِكَ ٱلۡعَذَابُۖ وَلَعَذَابُ ٱلۡأٓخِرَةِ أَكۡبَرُۚ لَوۡ كَانُواْ يَعۡلَمُونَ
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمۡ جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَنَجۡعَلُ ٱلۡمُسۡلِمِينَ كَٱلۡمُجۡرِمِينَ
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لَكُمۡ كِتَٰبٞ فِيهِ تَدۡرُسُونَ
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ لَكُمۡ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لَكُمۡ أَيۡمَٰنٌ عَلَيۡنَا بَٰلِغَةٌ إِلَىٰ يَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ إِنَّ لَكُمۡ لَمَا تَحۡكُمُونَ
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَلۡهُمۡ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لَهُمۡ شُرَكَآءُ فَلۡيَأۡتُواْ بِشُرَكَآئِهِمۡ إِن كَانُواْ صَٰدِقِينَ
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
يَوۡمَ يُكۡشَفُ عَن سَاقٖ وَيُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ فَلَا يَسۡتَطِيعُونَ
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۖ وَقَدۡ كَانُواْ يُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ وَهُمۡ سَٰلِمُونَ
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَذَرۡنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِۖ سَنَسۡتَدۡرِجُهُم مِّنۡ حَيۡثُ لَا يَعۡلَمُونَ
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأُمۡلِي لَهُمۡۚ إِنَّ كَيۡدِي مَتِينٌ
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ تَسۡـَٔلُهُمۡ أَجۡرٗا فَهُم مِّن مَّغۡرَمٖ مُّثۡقَلُونَ
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ عِندَهُمُ ٱلۡغَيۡبُ فَهُمۡ يَكۡتُبُونَ
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱصۡبِرۡ لِحُكۡمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ ٱلۡحُوتِ إِذۡ نَادَىٰ وَهُوَ مَكۡظُومٞ
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَّوۡلَآ أَن تَدَٰرَكَهُۥ نِعۡمَةٞ مِّن رَّبِّهِۦ لَنُبِذَ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ مَذۡمُومٞ
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱجۡتَبَٰهُ رَبُّهُۥ فَجَعَلَهُۥ مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِن يَكَادُ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لَيُزۡلِقُونَكَ بِأَبۡصَٰرِهِمۡ لَمَّا سَمِعُواْ ٱلذِّكۡرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُۥ لَمَجۡنُونٞ
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
 
Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Al-Qalam
Mục lục các chương Kinh Số trang
 
Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Dịch thuật tiếng Amharic - Mục lục các bản dịch

Bản dịch ý nghĩa nội dung Kinh Qur'an bằng tiếng Amharic, dịch thuật bởi Muhammad Sodiq và Muhammad Ath-Thany Habib. Bản dịch đã được kiểm duyệt bởi Trung tâm Dịch thuật Rowwad và bản dịch gốc hiện đang có sẵn cho tham khảo, đóng góp ý kiến, đánh giá để không ngừng nâng cao.

Đóng lại