Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Bản dịch tiếng Amharic - Zain * - Mục lục các bản dịch


Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Saffat   Câu:

ሱረቱ አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
52. (እንዲህ) የሚል: ‹በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
53. ‹በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆነ ጊዜ እኛ በእርግጥ እኛ እንመረመራለን?› የሚልም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
55. ይመለከታልም በገሀነም መካከልም ጓደኛውን ያየዋል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
56. ይላል «በአላህ እምላለሁ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር።» (ይላል)
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
58. (የገነት ሰዎች ይላሉ)፡ «እኛ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን?»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር እኛም የምንቀጣ አይደለንም» ይላሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
60.ይህ ለገነት ሰዎች የተወሳው እርሱ በእርግጥ ታላቅ እድል ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
61. ለዚህ ብጤ ሰሪዎች ሁሉ ይስሩ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ
63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
64. እርሷ ከገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
66. እነርሱ ከእርሷ በይዎች ናቸው:: ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
67. ከዚያ ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅልን መጠጥ አላቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
69. እነርሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋል።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
70. እነርሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
71. ከእነርሱም በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ ህዝቦች አብዛሀኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
72. በውስጣቸዉም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት!
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
75. ኑህም በእርግጥ ጠራን:: ምንኛ ያማርን ምላሽ ሰጪ ነን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
78. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝና ተውን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑህ ላይ ይሁን።»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
80. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
81. እርሱ ከአማኞች ባሮቻችን ነውና::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
82. ከዚያም ሌሎችን አሰመጥን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) ኢብራሂምም በእርግጥ ከወገኖቹ አንዱ ነው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
85. ለአባቱና ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ: «ምንን ትገዛላችሁ?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
87. «በዓለማቱ ጌታስ ሀሳባችሁ ምንድ ነው?።»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
88. በከዋክብት መመልከትን ተመለከተ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
89. እኔ «በሽተኛ ነኝ» አለ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
90. እነርሱም ከእርሱ የሸሹ ሆነው ሄዱ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
91. ከዚያ እሱ ወደ አማልዕክቶቻቸው ተዘነበለ፤ (እንዲህ) አለም፡- «አትበሉም እንዴ?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
92. «ምንም የማትናገሩበትስ ምን ምክኒያት አላችሁ?»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
93. በቀኝ (እጁ) የሚመታቸዉም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
94. ወደ እርሱም ሰዎቹ እየሮጡ መጡ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
95. አለ: «የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
96. «አላህ እናንተንም ሆነ የምትሰሩትን ሁሉ የፈጠረ ሲሆን» አላቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም።» አሉ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
98. ለእርሱ ተንኮልን አስቡ ወራዶችም አደረግናቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
99. አለም፡- «እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ፤ በእርግጥ ይመራኛልና።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
100. «ጌታየ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ።»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
101. ታጋሽም በሆነ ልጅም አበሰርነው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ
102. ከእርሱ ጋርም (ለስራ) በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ትላለህ?» አለው። «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ስራ፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ።» አለ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
104. ጠራነዉም: «ኢብራሂም ሆይ!
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
105. «ራዕዩን በርግጥ እውን አደረግክ።» እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
107. በታላቅ እርድም መስዕዋት ቤዛ አደረግንለት።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
110. ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
112. በኢስሐቅም አበሰርነው። ከመልካሞች የሆነ ነብይ ሲሆን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን። ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሰሪ አለ:: ነፍሱን በግልጽ በዳይም አለ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
114. በሙሳና በሀሩን ላይ በእርግጥ ለገስን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
115. እነርሱንም ሆነ ህዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
116. ረዳናቸውናም እነርሱ አሸናፊዎቹ ሆኑ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝናን ተውንላቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
120. ሰላም በሙሳና በሀሩን ላይ ይሁን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
121. እኛ ልክ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
122. ሁለቱም በትክክል በአላህ ካመኑት ባሮቻችን ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
124. ለህዝቦቹም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አላህን አትፈሩምን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
125. «ስዕልን ትገዛላችሁ? ከስዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነዉም አምላክ ትተዋላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
126. «አላህ ጌታችሁና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁንም ጌታ ትተዋላችሁን?»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
127. አስተባበሉትም ስለዚህ እነርሱ ለቅጣት የሚጣዱ ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
128. ንጹህ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
129. በእነርሱ ላይም በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
130. ሰላም በኢልያስ ላይ ይሁን፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
131. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
132. እርሱ በእርግጥ ከምዕመናን ባሮቻችን ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
133. ሉጥም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳናቸው ጊዜ (የሆነዉን አስታውስ)::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
135. በቅጣቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
137. (መኮች ሆይ)፤ እናንተም በእነርሱ መኖሪያዎች ላይ ያነጋችሁ ስትሆኑ ታልፋላችሁ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
138. በሌሊትም ታልፋላችሁ:: ልብ አታደርጉምን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
140. ወደ ተሞላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ አስታውስ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
141. እጣም ተጣጣለ፤ ከተሸነፉትም ሆነ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳ ነባሪው ዋጠው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነ ኖሮ
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው ባህር ዳርቻ ላይ ጣልነዉም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
146. በእርሱም ላይ በአጠገቡ ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
147. ወደ መቶ ሺህ ሰዎችም ላክነው፤ ከቶውንም ይጨምራሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
148. አመኑም። እስከ ጊዜው ድረስም አጣቀምናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ
149. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የመካን ሰዎች ጠይቃቸዉም: «ለጌታህ ሴት ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራሉን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ
150. «ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላዕክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ
151. አስተውሉ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው የተነሳ ይላሉ:
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
152.፡- «አላህ መላዕክትን ወለደ።» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ
153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጠን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
154. ለእናንተ ምን አስረጂ አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
155. አትገነዘቡምን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ
156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጂ አላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
157. «እውነተኞች እንደሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» በላቸው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ:: አጋንንትም ሆኑ ይህን ባዩች በእሳት የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ አውቀዋል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች በአላህ ላይ አይዋሹም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ
161. (ካሐዲያን ሆይ!) እናንተም የምትገዟቸዉም ሁሉ፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ
162. በእርሱ በአላህ ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ
163. ያንን እርሱ ገሀነም ገቢ የሆነውን ቢሆን እንጂ (አጥማሚዎች አይደላችሁም)።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ
164. (መላእክቶችም አሉ)? «ከእኛ አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ
165. «እኛም ጌታን ለመገዛት ተሰላፊዎቹ እኛ ነን።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ
166. «እኛም አላህን አጥሪዎቹ እኛው ነን።»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ
167. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱ (ከሓዲያን) በእርግጥ ይሉ ነበር:
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
168. «ከቀድሞዎቹ መጽሐፍ ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረ ኖሮ
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር።»
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
170. ግን ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ በእርሱ ላይ ካዱ። ወደ ፊትም በእርግጥ ያውቃሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ
171. የእርዳታ ቃላችንም መልዕክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ
172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ብቻ ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
174. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱም ከመካ ከሓዲያን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር ተዋቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
175. ተመልከታቸዉም ወደፊትም የሚደርስባቸውን ያያሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
176. በቅጣታችንም ያቻኩሉናልን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ
177. በቀያቸዉም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
178. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ተዋቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
180. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ
181. በመልዕክተኞቹም ላይ ሰላም ይሁን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
182. ምስጋና ሁሉም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይገባው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
 
Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Saffat
Mục lục các chương Kinh Số trang
 
Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Bản dịch tiếng Amharic - Zain - Mục lục các bản dịch

Bản dịch tiếng Amharic

Đóng lại