የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም * - የትርጉሞች ማዉጫ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አት ተክዊር   አንቀጽ:

ሱረቱ አት ተክዊር

إِذَا ٱلشَّمۡسُ كُوِّرَتۡ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتۡ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ سُيِّرَتۡ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡعِشَارُ عُطِّلَتۡ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡوُحُوشُ حُشِرَتۡ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ سُجِّرَتۡ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتۡ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡمَوۡءُۥدَةُ سُئِلَتۡ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بِأَيِّ ذَنۢبٖ قُتِلَتۡ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتۡ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ كُشِطَتۡ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡجَحِيمُ سُعِّرَتۡ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡجَنَّةُ أُزۡلِفَتۡ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّآ أَحۡضَرَتۡ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلۡخُنَّسِ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ٱلۡجَوَارِ ٱلۡكُنَّسِ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلَّيۡلِ إِذَا عَسۡعَسَ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَا تَنَفَّسَ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي ٱلۡعَرۡشِ مَكِينٖ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
مُّطَاعٖ ثَمَّ أَمِينٖ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجۡنُونٖ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡمُبِينِ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا هُوَ عَلَى ٱلۡغَيۡبِ بِضَنِينٖ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَيۡطَٰنٖ رَّجِيمٖ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَأَيۡنَ تَذۡهَبُونَ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنۡ هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَسۡتَقِيمَ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
 
የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አት ተክዊር
የምዕራፎች ማውጫ የገፅ ቁጥር
 
የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም - የትርጉሞች ማዉጫ

ወደ አማርኛ በሸይኽ ሙሓመድ ሷዲቅ እና በሸይኽ ሙሓመድ ሣኒ ሓቢብ የተተረጎመ የቁርዓን መልዕክተ ትርጉም። በሩዋድ የትርጉም ማእከልም ተቆጣጣሪነት ማስተካከያ ተደርጎበታል። ዋናው የትርጉም ቅጅም ለአስተያየቶች፣ ተከታታይ ግምገማ እና መሻሻል ቀርቧል።

መዝጋት