আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ফজৰ   আয়াত:

ሱረቱ አል ፈጅር

وَٱلۡفَجۡرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَيَالٍ عَشۡرٖ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلشَّفۡعِ وَٱلۡوَتۡرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَسۡرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
هَلۡ فِي ذَٰلِكَ قَسَمٞ لِّذِي حِجۡرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَلَمۡ تَرَ كَيۡفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُواْ ٱلصَّخۡرَ بِٱلۡوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفِرۡعَوۡنَ ذِي ٱلۡأَوۡتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ٱلَّذِينَ طَغَوۡاْ فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَكۡثَرُواْ فِيهَا ٱلۡفَسَادَ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَصَبَّ عَلَيۡهِمۡ رَبُّكَ سَوۡطَ عَذَابٍ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلۡمِرۡصَادِ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَمَّا ٱلۡإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكۡرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَكۡرَمَنِ
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيۡهِ رِزۡقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَهَٰنَنِ
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّاۖ بَل لَّا تُكۡرِمُونَ ٱلۡيَتِيمَ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَا تَحَٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتَأۡكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكۡلٗا لَّمّٗا
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتُحِبُّونَ ٱلۡمَالَ حُبّٗا جَمّٗا
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّآۖ إِذَا دُكَّتِ ٱلۡأَرۡضُ دَكّٗا دَكّٗا
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلۡمَلَكُ صَفّٗا صَفّٗا
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤ @সংশোধনকৃত
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَجِاْيٓءَ يَوۡمَئِذِۭ بِجَهَنَّمَۚ يَوۡمَئِذٖ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكۡرَىٰ
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
يَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي قَدَّمۡتُ لِحَيَاتِي
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٞ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٞ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
يَٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفۡسُ ٱلۡمُطۡمَئِنَّةُ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ٱرۡجِعِيٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةٗ مَّرۡضِيَّةٗ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَٱدۡخُلِي فِي عِبَٰدِي
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱدۡخُلِي جَنَّتِي
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ফজৰ
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

বন্ধ