Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Firo amhariiwo * - Tippudi firooji ɗii

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Firo maanaaji Simoore: Simoore juremdeero   Aaya:

ሱረቱ አር ረሕማን

ٱلرَّحۡمَٰنُ
አል-ረሕማን፤
Faccirooji aarabeeji:
عَلَّمَ ٱلۡقُرۡءَانَ
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ
ሰውን ፈጠረ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
عَلَّمَهُ ٱلۡبَيَانَ
መናገርን አስተማረው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ بِحُسۡبَانٖ
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلنَّجۡمُ وَٱلشَّجَرُ يَسۡجُدَانِ
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلسَّمَآءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ ٱلۡمِيزَانَ
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَلَّا تَطۡغَوۡاْ فِي ٱلۡمِيزَانِ
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَقِيمُواْ ٱلۡوَزۡنَ بِٱلۡقِسۡطِ وَلَا تُخۡسِرُواْ ٱلۡمِيزَانَ
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلۡأَرۡضَ وَضَعَهَا لِلۡأَنَامِ
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فِيهَا فَٰكِهَةٞ وَٱلنَّخۡلُ ذَاتُ ٱلۡأَكۡمَامِ
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلۡحَبُّ ذُو ٱلۡعَصۡفِ وَٱلرَّيۡحَانُ
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِن صَلۡصَٰلٖ كَٱلۡفَخَّارِ
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَخَلَقَ ٱلۡجَآنَّ مِن مَّارِجٖ مِّن نَّارٖ
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقَيۡنِ وَرَبُّ ٱلۡمَغۡرِبَيۡنِ
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
مَرَجَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ يَلۡتَقِيَانِ
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
بَيۡنَهُمَا بَرۡزَخٞ لَّا يَبۡغِيَانِ
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Faccirooji aarabeeji:
يَخۡرُجُ مِنۡهُمَا ٱللُّؤۡلُؤُ وَٱلۡمَرۡجَانُ
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
وَلَهُ ٱلۡجَوَارِ ٱلۡمُنشَـَٔاتُ فِي ٱلۡبَحۡرِ كَٱلۡأَعۡلَٰمِ
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
كُلُّ مَنۡ عَلَيۡهَا فَانٖ
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَيَبۡقَىٰ وَجۡهُ رَبِّكَ ذُو ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
يَسۡـَٔلُهُۥ مَن فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ كُلَّ يَوۡمٍ هُوَ فِي شَأۡنٖ
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Faccirooji aarabeeji:
سَنَفۡرُغُ لَكُمۡ أَيُّهَ ٱلثَّقَلَانِ
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
يَٰمَعۡشَرَ ٱلۡجِنِّ وَٱلۡإِنسِ إِنِ ٱسۡتَطَعۡتُمۡ أَن تَنفُذُواْ مِنۡ أَقۡطَارِ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ فَٱنفُذُواْۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلۡطَٰنٖ
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
يُرۡسَلُ عَلَيۡكُمَا شُوَاظٞ مِّن نَّارٖ وَنُحَاسٞ فَلَا تَنتَصِرَانِ
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فَإِذَا ٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ وَرۡدَةٗ كَٱلدِّهَانِ
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُسۡـَٔلُ عَن ذَنۢبِهِۦٓ إِنسٞ وَلَا جَآنّٞ
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
يُعۡرَفُ ٱلۡمُجۡرِمُونَ بِسِيمَٰهُمۡ فَيُؤۡخَذُ بِٱلنَّوَٰصِي وَٱلۡأَقۡدَامِ
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
هَٰذِهِۦ جَهَنَّمُ ٱلَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا ٱلۡمُجۡرِمُونَ
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
يَطُوفُونَ بَيۡنَهَا وَبَيۡنَ حَمِيمٍ ءَانٖ
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
وَلِمَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ جَنَّتَانِ
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
ذَوَاتَآ أَفۡنَانٖ
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِمَا عَيۡنَانِ تَجۡرِيَانِ
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِمَا مِن كُلِّ فَٰكِهَةٖ زَوۡجَانِ
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ فُرُشِۭ بَطَآئِنُهَا مِنۡ إِسۡتَبۡرَقٖۚ وَجَنَى ٱلۡجَنَّتَيۡنِ دَانٖ
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِنَّ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
كَأَنَّهُنَّ ٱلۡيَاقُوتُ وَٱلۡمَرۡجَانُ
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
هَلۡ جَزَآءُ ٱلۡإِحۡسَٰنِ إِلَّا ٱلۡإِحۡسَٰنُ
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Faccirooji aarabeeji:
مُدۡهَآمَّتَانِ
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِمَا عَيۡنَانِ نَضَّاخَتَانِ
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِمَا فَٰكِهَةٞ وَنَخۡلٞ وَرُمَّانٞ
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
فِيهِنَّ خَيۡرَٰتٌ حِسَانٞ
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
حُورٞ مَّقۡصُورَٰتٞ فِي ٱلۡخِيَامِ
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ رَفۡرَفٍ خُضۡرٖ وَعَبۡقَرِيٍّ حِسَانٖ
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Faccirooji aarabeeji:
تَبَٰرَكَ ٱسۡمُ رَبِّكَ ذِي ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
 
Firo maanaaji Simoore: Simoore juremdeero
Tippudi cimooje Tonngoode hello ngoo
 
Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Firo amhariiwo - Tippudi firooji ɗii

Firo maaniiwo al-quraan tedduɗo oo fayde e ɗemngal amhari, firi ɗum ko Mawɗo Muhammad Saadiq e Muhammad ɗiɗaɓo Habiib. Ngo feewnitaama e njiimaandi hentorde kanngameeji firo, inanewnaa ƴellitaade e firo asliiwo ngoo mgam feññinde yiyannde e horo kam e ƴellito duumiingo.

Uddude