Përkthimi i kuptimeve të Kuranit Fisnik - الترجمة الأمهرية - زين * - Përmbajtja e përkthimeve


Përkthimi i kuptimeve Surja: Suretu En Nexhm   Ajeti:

ሱረቱ አን ነጅም

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤
Tefsiret në gjuhën arabe:
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።
Tefsiret në gjuhën arabe:
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤
Tefsiret në gjuhën arabe:
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::
Tefsiret në gjuhën arabe:
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::
Tefsiret në gjuhën arabe:
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::
Tefsiret në gjuhën arabe:
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።
Tefsiret në gjuhën arabe:
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።
Tefsiret në gjuhën arabe:
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::
Tefsiret në gjuhën arabe:
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::
Tefsiret në gjuhën arabe:
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::
Tefsiret në gjuhën arabe:
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
53.የተገለበጡትንም ደፋ።
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
54. ባሸፈናት ሸፈናት::
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
57. ቀራቢቱም ቀረበች::
Tefsiret në gjuhën arabe:
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?
Tefsiret në gjuhën arabe:
فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩
62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::
Tefsiret në gjuhën arabe:
 
Përkthimi i kuptimeve Surja: Suretu En Nexhm
Përmbajtja e sureve Numri i faqes
 
Përkthimi i kuptimeve të Kuranit Fisnik - الترجمة الأمهرية - زين - Përmbajtja e përkthimeve

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

Mbyll