Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Bản dịch tiếng Amharic - Zain * - Mục lục các bản dịch


Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Al-Najm   Câu:

ሱረቱ አን ነጅም

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
53.የተገለበጡትንም ደፋ።
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
54. ባሸፈናት ሸፈናት::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
57. ቀራቢቱም ቀረበች::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩
62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::
Các Tafsir tiếng Ả-rập:
 
Ý nghĩa nội dung Chương: Chương Al-Najm
Mục lục các chương Kinh Số trang
 
Bản dịch ý nghĩa nội dung Qur'an - Bản dịch tiếng Amharic - Zain - Mục lục các bản dịch

Bản dịch tiếng Amharic

Đóng lại