Salin ng mga Kahulugan ng Marangal na Qur'an - Salin sa Wikang Amhariko * - Indise ng mga Salin

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Salin ng mga Kahulugan Surah: Al-Qiyāmah   Ayah:

ሱረቱ አል ቂያማህ

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
Ang mga Tafsir na Arabe:
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
كَلَّا لَا وَزَرَ
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
Ang mga Tafsir na Arabe:
أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
Ang mga Tafsir na Arabe:
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
Ang mga Tafsir na Arabe:
أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
Ang mga Tafsir na Arabe:
 
Salin ng mga Kahulugan Surah: Al-Qiyāmah
Indise ng mga Surah Numero ng Pahina
 
Salin ng mga Kahulugan ng Marangal na Qur'an - Salin sa Wikang Amhariko - Indise ng mga Salin

Salin ng mga Kahulugan ng Marangal na Qur'an sa wikang Amhariko. Isinalin ito nina Shaykh Muhammad Sadiq at Muhammad Sani Habib. Imprenta ng taong 2011. Isinagawa ang pagtatama nito sa pangangasiwa ng Sentro ng Rowad sa Pagsasalin. Pinapayagan ang pagtingin sa orihinal na salin sa layuning magpahayag ng pananaw, magsiyasat, at patuloy na paglinang.

Isara