ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية * - فهرس التراجم

XML CSV Excel API
تنزيل الملفات يتضمن الموافقة على هذه الشروط والسياسات

ترجمة معاني سورة: النبإ   آية:

سورة النبإ - ሱረቱ አን ነበእ

عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
التفاسير العربية:
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
التفاسير العربية:
ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
التفاسير العربية:
كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
التفاسير العربية:
ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
التفاسير العربية:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
التفاسير العربية:
وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
التفاسير العربية:
وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
التفاسير العربية:
وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
التفاسير العربية:
وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
التفاسير العربية:
وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
التفاسير العربية:
وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
التفاسير العربية:
وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
التفاسير العربية:
لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
التفاسير العربية:
وَجَنَّٰتٍ أَلۡفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
التفاسير العربية:
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
التفاسير العربية:
وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
التفاسير العربية:
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابٗا
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
التفاسير العربية:
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
التفاسير العربية:
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
التفاسير العربية:
إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
التفاسير العربية:
جَزَآءٗ وِفَاقًا
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
التفاسير العربية:
وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
التفاسير العربية:
وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
التفاسير العربية:
فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
التفاسير العربية:
حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
التفاسير العربية:
وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
التفاسير العربية:
وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
التفاسير العربية:
لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّٰبٗا
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
التفاسير العربية:
جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
التفاسير العربية:
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
التفاسير العربية:
يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
التفاسير العربية:
ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
 
ترجمة معاني سورة: النبإ
فهرس السور رقم الصفحة
 
ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - فهرس التراجم

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

إغلاق