Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation * - Translations’ Index

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Translation of the meanings Surah: An-Naba’   Ayah:

ሱረቱ አን ነበእ

عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
Arabic explanations of the Qur’an:
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
Arabic explanations of the Qur’an:
وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَنَّٰتٍ أَلۡفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابٗا
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
جَزَآءٗ وِفَاقًا
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّٰبٗا
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: An-Naba’
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Translations’ Index

Translation of the Quran meanings into Amharic by Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib. Corrected by supervision of Rowwad Translation Center. The original translation is available for suggestions, continuous evaluation and development.

close