કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - અમ્હેરિક ભાષાતર * - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: અલ્ હાકકહ   આયત:

ሱረቱ አል ሓቃህ

ٱلۡحَآقَّةُ
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
અરબી તફસીરો:
مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
અરબી તફસીરો:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
અરબી તફસીરો:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
અરબી તફસીરો:
وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
અરબી તફસીરો:
سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
અરબી તફસીરો:
وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
અરબી તફસીરો:
إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
અરબી તફસીરો:
لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
અરબી તફસીરો:
وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
અરબી તફસીરો:
وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
અરબી તફસીરો:
وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
અરબી તફસીરો:
يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
અરબી તફસીરો:
فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
અરબી તફસીરો:
إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
અરબી તફસીરો:
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
અરબી તફસીરો:
فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
અરબી તફસીરો:
قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
અરબી તફસીરો:
كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
અરબી તફસીરો:
وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
અરબી તફસીરો:
وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
અરબી તફસીરો:
يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
અરબી તફસીરો:
مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
અરબી તફસીરો:
هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
અરબી તફસીરો:
خُذُوهُ فَغُلُّوهُ
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
અરબી તફસીરો:
ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
અરબી તફસીરો:
ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
અરબી તફસીરો:
إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
અરબી તફસીરો:
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
અરબી તફસીરો:
فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
અરબી તફસીરો:
وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
અરબી તફસીરો:
لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
અરબી તફસીરો:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
અરબી તફસીરો:
وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ
በማታዩትም ነገር፡፡
અરબી તફસીરો:
إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
અરબી તફસીરો:
وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
અરબી તફસીરો:
وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
અરબી તફસીરો:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
અરબી તફસીરો:
وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
અરબી તફસીરો:
لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ
በቀኝ በያዝነው ነበር፡፡
અરબી તફસીરો:
ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
અરબી તફસીરો:
فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
અરબી તફસીરો:
وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
અરબી તફસીરો:
وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
અરબી તફસીરો:
وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
અરબી તફસીરો:
وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
અરબી તફસીરો:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
અરબી તફસીરો:
 
શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: અલ્ હાકકહ
સૂરહ માટે અનુક્રમણિકા પેજ નંબર
 
કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - અમ્હેરિક ભાષાતર - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા

અમહેરીક ભાષામાં કુરઆન મજીદનું ભાષાતર, તેનું ભાષાતર મુહમ્મદ સાદિક અને હબીબ દ્વારા કરવામાં આવ્યું, આયતોમાં સુધારો મરકઝ રવાદ અત્ તરજમા દ્વારા કરવામાં આવ્યો છે, મૂળ અનુવાદ, આપના અભિપ્રાય તેમજ મુકલ્યાંકન અને સતત સુધારા કરવા માટે ઉપલબ્ધ છે.

બંધ કરો