وه‌رگێڕانی ماناكانی قورئانی پیرۆز - وەرگێڕاوی ئەمهەری - زەین * - پێڕستی وه‌رگێڕاوه‌كان


وه‌رگێڕانی ماناكان سوره‌تی: سورەتی المدثر   ئایه‌تی:

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!
تەفسیرە عەرەبیەکان:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
3. ጌታህንም አክብር::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
4. ልብስህንም አጥራ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
5. ጣዖትንም ራቅ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ نَظَرَ
21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)
تەفسیرە عەرەبیەکان:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
تەفسیرە عەرەبیەکان:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
51. ከአንበሳ የሸሹ
تەفسیرە عەرەبیەکان:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
 
وه‌رگێڕانی ماناكان سوره‌تی: سورەتی المدثر
پێڕستی سوره‌ته‌كان ژمارەی پەڕە
 
وه‌رگێڕانی ماناكانی قورئانی پیرۆز - وەرگێڕاوی ئەمهەری - زەین - پێڕستی وه‌رگێڕاوه‌كان

وەرگێڕاوی ئەمهەری

داخستن