Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Amharų k. vertimas - Zain * - Vertimų turinys


Reikšmių vertimas Sūra: Sūra Al-Muddassir   Aja (Korano eilutė):

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!
Tafsyrai arabų kalba:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
3. ጌታህንም አክብር::
Tafsyrai arabų kalba:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
4. ልብስህንም አጥራ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
5. ጣዖትንም ራቅ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።
Tafsyrai arabų kalba:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤
Tafsyrai arabų kalba:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።
Tafsyrai arabų kalba:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።
Tafsyrai arabų kalba:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።
Tafsyrai arabų kalba:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤
Tafsyrai arabų kalba:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::
Tafsyrai arabų kalba:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።
Tafsyrai arabų kalba:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።
Tafsyrai arabų kalba:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!
Tafsyrai arabų kalba:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!
Tafsyrai arabų kalba:
ثُمَّ نَظَرَ
21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።
Tafsyrai arabų kalba:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::
Tafsyrai arabų kalba:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::
Tafsyrai arabų kalba:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::
Tafsyrai arabų kalba:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
Tafsyrai arabų kalba:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::
Tafsyrai arabų kalba:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።
Tafsyrai arabų kalba:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::
Tafsyrai arabų kalba:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤
Tafsyrai arabų kalba:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤
Tafsyrai arabų kalba:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤
Tafsyrai arabų kalba:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።
Tafsyrai arabų kalba:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤
Tafsyrai arabų kalba:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::
Tafsyrai arabų kalba:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::
Tafsyrai arabų kalba:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)
Tafsyrai arabų kalba:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
Tafsyrai arabų kalba:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።
Tafsyrai arabų kalba:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።
Tafsyrai arabų kalba:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።
Tafsyrai arabų kalba:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤
Tafsyrai arabų kalba:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ
Tafsyrai arabų kalba:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።
Tafsyrai arabų kalba:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?
Tafsyrai arabų kalba:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
51. ከአንበሳ የሸሹ
Tafsyrai arabų kalba:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::
Tafsyrai arabų kalba:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::
Tafsyrai arabų kalba:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።
Tafsyrai arabų kalba:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::
Tafsyrai arabų kalba:
 
Reikšmių vertimas Sūra: Sūra Al-Muddassir
Sūrų turinys Puslapio numeris
 
Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Amharų k. vertimas - Zain - Vertimų turinys

Amharų k. vertimas

Uždaryti