Check out the new design

قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہاری ترجمہ - افریقہ اکیڈمی * - ترجمے کی لسٹ

PDF XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

معانی کا ترجمہ سورت: بقرہ   آیت:
وَقَالُواْ كُونُواْ هُودًا أَوۡ نَصَٰرَىٰ تَهۡتَدُواْۗ قُلۡ بَلۡ مِلَّةَ إِبۡرَٰهِـۧمَ حَنِيفٗاۖ وَمَا كَانَ مِنَ ٱلۡمُشۡرِكِينَ
135. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አይሁድና ክርስቲያኖች በየበኩላቸው “አይሁድ ወይም ክርስቲያን ሁኑ ቅንን መንገድ ትመራላችሁና” አሉ:: “አይደለም ይልቁንም የኢብራሂምን ሀይማኖት ቀጥተኛ ሲሆን እንከተላለን፣ ኢብራሂምም ከአጋሪዎችም አልነበረም” በላቸው::
عربی تفاسیر:
قُولُوٓاْ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ وَمَآ أُنزِلَ إِلَيۡنَا وَمَآ أُنزِلَ إِلَىٰٓ إِبۡرَٰهِـۧمَ وَإِسۡمَٰعِيلَ وَإِسۡحَٰقَ وَيَعۡقُوبَ وَٱلۡأَسۡبَاطِ وَمَآ أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَآ أُوتِيَ ٱلنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمۡ لَا نُفَرِّقُ بَيۡنَ أَحَدٖ مِّنۡهُمۡ وَنَحۡنُ لَهُۥ مُسۡلِمُونَ
136. (እናንተ ያመናችሁ ሆይ!) «በአላህና ወደ እኛ በተወረደው ቁርኣን ወደ ኢብራሂምም፣ ወደ ኢስማዒልም፣ ወደ ኢስሀቅም፣ ወደ የዕቁብና ወደ ነገዶችም በተወረደው መለኮታዊ መልዕክት ሁሉ በዚያም ሙሳና ዒሳ በተሰጡት፤ በዚያም ነብያት ሁሉ ከጌታቸው በተለገሱት ከእነርሱ አንዱን ከሌላው የማንለይ ስንሆን አመንን:: እኛም (ለአላህ) ፍጹም ታዛዦች ነን።» በሉ።
عربی تفاسیر:
فَإِنۡ ءَامَنُواْ بِمِثۡلِ مَآ ءَامَنتُم بِهِۦ فَقَدِ ٱهۡتَدَواْۖ وَّإِن تَوَلَّوۡاْ فَإِنَّمَا هُمۡ فِي شِقَاقٖۖ فَسَيَكۡفِيكَهُمُ ٱللَّهُۚ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ
137. (እናንተ ያመናችሁ ሆይ!) እናንተ ባመናችሁበት መልኩ ካመኑ በእርግጥ በትክክለኛው ጎዳና ላይ ናቸው:: ከእርሱ ካፈነገጡ ግን እነርሱ በጭቅጭቅ ውስጥ ብቻ ናቸው:: የእነርሱንም ተንኮል አላህ ይበቃሀል:: እርሱም ሁሉን ሰሚና ሁሉንም አዋቂ ነውና።
عربی تفاسیر:
صِبۡغَةَ ٱللَّهِ وَمَنۡ أَحۡسَنُ مِنَ ٱللَّهِ صِبۡغَةٗۖ وَنَحۡنُ لَهُۥ عَٰبِدُونَ
138. የአላህን የተፈጥሮ መንከር (እምነት) ያዙ:: በመንከርም ከአላህ ይበልጥ ያማረ ማነው? (ማንም የለም):: እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን (በሉ)፡፡
عربی تفاسیر:
قُلۡ أَتُحَآجُّونَنَا فِي ٱللَّهِ وَهُوَ رَبُّنَا وَرَبُّكُمۡ وَلَنَآ أَعۡمَٰلُنَا وَلَكُمۡ أَعۡمَٰلُكُمۡ وَنَحۡنُ لَهُۥ مُخۡلِصُونَ
139. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አላህ ጌታችንና ጌታችሁ ሲሆን ለእኛም ስራችን ያለን ስንሆን ለእናንተም ስራችሁ ያላችሁ ስትሆኑ እኛም ስራችንን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች ሆነን ሳለን በአላህ (ሀይማኖት) ትከራከሩናላችሁን?» በላቸው።
عربی تفاسیر:
أَمۡ تَقُولُونَ إِنَّ إِبۡرَٰهِـۧمَ وَإِسۡمَٰعِيلَ وَإِسۡحَٰقَ وَيَعۡقُوبَ وَٱلۡأَسۡبَاطَ كَانُواْ هُودًا أَوۡ نَصَٰرَىٰۗ قُلۡ ءَأَنتُمۡ أَعۡلَمُ أَمِ ٱللَّهُۗ وَمَنۡ أَظۡلَمُ مِمَّن كَتَمَ شَهَٰدَةً عِندَهُۥ مِنَ ٱللَّهِۗ وَمَا ٱللَّهُ بِغَٰفِلٍ عَمَّا تَعۡمَلُونَ
140. ወይስ «ኢብራሂምም፣ ኢስማዒልም፣ ኢስሐቅም፣ ያዕቆብም፣ እንዲሁም ነገዶቹም አይሁድ ወይም ክርስቲያኖች ነበሩ» ትላላችሁን? (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) “እናንተ ናችሁ የምታውቁት? ወይንስ አላህ?” በላቸው:: እርሱ ዘንድ ከአላህ የሆነችን ምስክርነት ከደበቀ ይበልጥ አጥፊ ማነው? አላህ የምትፈጽሙትን ሁሉ ዘንጊ አይደለም።
عربی تفاسیر:
تِلۡكَ أُمَّةٞ قَدۡ خَلَتۡۖ لَهَا مَا كَسَبَتۡ وَلَكُم مَّا كَسَبۡتُمۡۖ وَلَا تُسۡـَٔلُونَ عَمَّا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
141. እነዚህ ያለፉ ሕዝቦች ናቸው:: ለእነርሱ የሰሩት አላቸው:: ለእናንተም የሰራችሁት አላችሁ:: እነርሱ ይሰሩት ከነበሩት ሁሉ አትጠየቁም::
عربی تفاسیر:
 
معانی کا ترجمہ سورت: بقرہ
سورتوں کی لسٹ صفحہ نمبر
 
قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہاری ترجمہ - افریقہ اکیڈمی - ترجمے کی لسٹ

محمد زین زہر الدین نے ترجمہ کیا۔ افریقہ اکیڈمی کی جانب سے شائع ہوا۔

بند کریں