Check out the new design

ការបកប្រែអត្ថន័យគួរអាន - ការបកប្រែជាភាសាអាំហារីច - អាឃាដេមីអាហ្វ្រិកា * - សន្ទស្សន៍នៃការបកប្រែ

PDF XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

ការបកប្រែអត្ថន័យ ជំពូក​: អាល់ហ្ពាក៏រ៉ោះ   អាយ៉ាត់:
قَالُواْ ٱدۡعُ لَنَا رَبَّكَ يُبَيِّن لَّنَا مَا هِيَ إِنَّ ٱلۡبَقَرَ تَشَٰبَهَ عَلَيۡنَا وَإِنَّآ إِن شَآءَ ٱللَّهُ لَمُهۡتَدُونَ
70. ጌታህን ጠይቅልን :: እርሷ ምን እንደሆነች ይግለጽልን:: ምክንያቱም ላሞቹ በሙሉ በእኛ ላይ ተመሳሰሉብን:: እኛም አላህ የሻ እንደሆነ በእርግጥ (ትክክለኛውን አቅጣጫ የምንይዝ) ተመሪዎች ነን” አሉ፡፡
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
قَالَ إِنَّهُۥ يَقُولُ إِنَّهَا بَقَرَةٞ لَّا ذَلُولٞ تُثِيرُ ٱلۡأَرۡضَ وَلَا تَسۡقِي ٱلۡحَرۡثَ مُسَلَّمَةٞ لَّا شِيَةَ فِيهَاۚ قَالُواْ ٱلۡـَٰٔنَ جِئۡتَ بِٱلۡحَقِّۚ فَذَبَحُوهَا وَمَا كَادُواْ يَفۡعَلُونَ
71. እርሱም: «‹እርሷ ያልተገራች ምድርን በማረስ የማታስነሳ፤ እርሻንም የማታጠጣ፤ ከነውር ሁሉ ነፃ የሆነች፤ ጸያፍ ምልክት የሌለባት ናት።› ይላችኋል አላቸው።» እነርሱም «አሁን ገና በትክክል መጣህ።» አሉ:: ከዚያ ትዕዛዙን ላለመፈጸም የቀረቡ ሆነው ላሟን አረዷት።
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
وَإِذۡ قَتَلۡتُمۡ نَفۡسٗا فَٱدَّٰرَٰءۡتُمۡ فِيهَاۖ وَٱللَّهُ مُخۡرِجٞ مَّا كُنتُمۡ تَكۡتُمُونَ
72. (የኢስራኢል ልጆች ሆይ!) ነፍስ በገደላችሁና በእርሷም ጉዳይ በተከራከራችሁ ጊዜ የሆነውን ታሪክ አስታውሱ:: አላህ ያን በውስጣችሁ ትደብቁት የነበራችሁትን ሚስጢር ሁሉ ገላጭ ነው፡፡
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
فَقُلۡنَا ٱضۡرِبُوهُ بِبَعۡضِهَاۚ كَذَٰلِكَ يُحۡيِ ٱللَّهُ ٱلۡمَوۡتَىٰ وَيُرِيكُمۡ ءَايَٰتِهِۦ لَعَلَّكُمۡ تَعۡقِلُونَ
73. (የሙቱን በድን) «በታረደችው ላም ከፊል አካል ምቱት አልን »:: (እናም መቱትና ተነሳ:: የገደለው ማን እንደሆነ ነገራቸውና እንደገና ሞተ::) ሰዎች ሆይ! ልክ እንደዚሁ ትገነዘቡና ታውቁ ዘንድ ሙታንን ህያው በማድረግ ተዓምራቶቹን ያሳያችኋል፡፡
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
ثُمَّ قَسَتۡ قُلُوبُكُم مِّنۢ بَعۡدِ ذَٰلِكَ فَهِيَ كَٱلۡحِجَارَةِ أَوۡ أَشَدُّ قَسۡوَةٗۚ وَإِنَّ مِنَ ٱلۡحِجَارَةِ لَمَا يَتَفَجَّرُ مِنۡهُ ٱلۡأَنۡهَٰرُۚ وَإِنَّ مِنۡهَا لَمَا يَشَّقَّقُ فَيَخۡرُجُ مِنۡهُ ٱلۡمَآءُۚ وَإِنَّ مِنۡهَا لَمَا يَهۡبِطُ مِنۡ خَشۡيَةِ ٱللَّهِۗ وَمَا ٱللَّهُ بِغَٰفِلٍ عَمَّا تَعۡمَلُونَ
74. ከዚያም ልቦቻቸው ከዚህ (ትዕይንት) በኋላ ደረቁ:: እርሷም በድርቅና እንደ አለት ድንጋዩች ወይም ከእርሱ ይበልጥ የበረቱ ናቸው:: ምክንያቱም ከድንጋዩች መካከል ጅረቶች (ወንዞች) የሚፈሱበት፤ ከእነርሱም የሚሰነጥቅና ከእርሱ ውሃ ምንጭ የሚወጣው፤ ከእነርሱም አላህን ከመፍራቱ የተነሳ ወደ ታች የሚወርድ አለና:: አላህ ከምትሰሩት ነገር ሁሉ ከአንዱም ዘንጊ አይደለም፡፡
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
۞ أَفَتَطۡمَعُونَ أَن يُؤۡمِنُواْ لَكُمۡ وَقَدۡ كَانَ فَرِيقٞ مِّنۡهُمۡ يَسۡمَعُونَ كَلَٰمَ ٱللَّهِ ثُمَّ يُحَرِّفُونَهُۥ مِنۢ بَعۡدِ مَا عَقَلُوهُ وَهُمۡ يَعۡلَمُونَ
75. ከ(አይሁድ) መካከል የአላህን ቃል የሚሰሙና ከዚያም እውነቱን ከተረዱ በኋላ ሆን ብለው እነርሱ እያወቁ የሚለውጡት ቡድኖች እያሉ ለእናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን?
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
وَإِذَا لَقُواْ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ قَالُوٓاْ ءَامَنَّا وَإِذَا خَلَا بَعۡضُهُمۡ إِلَىٰ بَعۡضٖ قَالُوٓاْ أَتُحَدِّثُونَهُم بِمَا فَتَحَ ٱللَّهُ عَلَيۡكُمۡ لِيُحَآجُّوكُم بِهِۦ عِندَ رَبِّكُمۡۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
76. እነዚያም ያመኑትን ሙስሊሞችን ባገኙ ጊዜ “እኛም እንደናንተው አምነናል” ይላሉ:: እርስ በርሳቸው ብቻ በተገናኙ ጊዜ ግን “አላህ በእናንተ ላይ የገለጸላችሁን ነገር በጌታችሁ ዘንድ እርሱን መረጃ እንዲያቀርቡባችሁ ትነግሯቸዋላችሁን? አታስተውሉምን?” ይባባላሉ::
តាហ្វសៀរជាភាសា​អារ៉ាប់ជាច្រេីន:
 
ការបកប្រែអត្ថន័យ ជំពូក​: អាល់ហ្ពាក៏រ៉ោះ
សន្ទស្សន៍នៃជំពូក លេខ​ទំព័រ
 
ការបកប្រែអត្ថន័យគួរអាន - ការបកប្រែជាភាសាអាំហារីច - អាឃាដេមីអាហ្វ្រិកា - សន្ទស្សន៍នៃការបកប្រែ

ការបកប្រែដោយ ម៉ូហាំម៉ាត់​ សេន សហ៊ឌីន។ ចេញផ្សាយដោយ វិទ្យាស្ថានអាហ្វ្រិក។

បិទ